No media source currently available
ባለፈው ወር የተቀሰቀሰውን የሱዳን ትጥቃዊ ግጭት እየሸሹ፣ በኢትዮጵያ የድንበር ከተማ በመተማ በኩል ብቻ፣ ከ20ሺሕ400 በላይ ፍልሰተኞች እንደገቡና ከእነርሱም የሚበዙት ኢትዮጵያውያን እንደኾኑ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ(OCHA) አስታውቋል።