በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳ ጥገኝነት ጠያቂዎችን የተመለከተ ስምምነት ይፋ አደረጉ


ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳ ጥገኝነት ጠያቂዎችን የተመለከተ ስምምነት ይፋ አደረጉ
ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳ ጥገኝነት ጠያቂዎችን የተመለከተ ስምምነት ይፋ አደረጉ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን እና የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጥገኝነት ጠያቂዎች የዩኤስ-ካናዳ ድንበርን መደበኛ ባልሆነ መንገድ እንዳያቋርጡ የሚያግድ ስደተኞችን የሚመለከት ስምምነት አርብ ዕለት ይፋ አድርገዋል ።

ፕሬዚደንት ከሆኑ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ካናዳ ያቀኑት ባይደን በቀጠናው ያለውን "በታሪክ ሊጠቀስ የሚችል የስደት ደረጃ " እልባት ለመስጠት ሁለቱ ሀገራት እየሰሩ መሆኑን በኦታዋ በነበረ የሁለትዮሽ የጋዜጠኞች ማስገንዘቢያ ላይ ተናግረዋል ።

ስደተኞችን የሚመለከተው ስምምነት እያንዳንዱ ሀገር ይፋዊ ባልሆኑ ማቋረጫዎች ወደ ድንበሩ የሚደርሱ ጥገኝነት ጠያቂዎችን እንዲመልስ የሚፈቅድ ሲሆን ፣ ካናዳ በየዩናይትድ ስቴትስ በኩል አልፈው ወደ ግዛቶቿ የሚገቡ ጥገኝነት ጠያቂዎች ቁጥር ለመገደብ እንደሚረዳት ተነግሯል ።

በቀደመው ስደተኞችን የሚመለከት ስምምነት የአሜሪካ እና የካናዳ ባለስልጣናት በሁለቱም አቅጣጫዎች በሚገኙ መደበኛ መግቢያ ቦታዎች በኩል የሚመጡ ጥገኝነት ጠያቂዎችን መመለስ ችለዋል።ነገር ግን ይህ አሰራር ኦፊሴላዊ ባልሆኑ መሻገሪያዎች ላይ ሳይተገበር ቆይቷል ።

"ደህንነቱ የተጠበቀ የሶስተኛ ሀገር ስምምነት" ተብሎ በሚጠራው ስምምነት መደበኛ ባልሆኑ መተላላፊያዎች የሚያቋርጡ ስደተኞች ይካተቱ ዘንድ ካናዳ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ግፊት ስታደርግ ቆይታለች ።

XS
SM
MD
LG