በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ደቡብ ክልል ውስጥ ከሁለት ሚሊየን በላይ ሰው እርዳታ ይጠብቃል


ደቡብ ክልል ውስጥ ከሁለት ሚሊየን በላይ ሰው እርዳታ ይጠብቃል
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:04 0:00

ደቡብ ክልል ውስጥ ከሁለት ሚሊየን በላይ ሰው እርዳታ ይጠብቃል

በደቡብ ክልል አማሮ ልዩ ወረዳ በተከሰተ ድርቅ አብዛኛው የወረዳው ነዋሪዎች ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውንና ከብቶቻቸውም እየሞቱባቸው መሆኑን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

ከድርቁ በተጨማሪ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም አለመኖሩ ጉዳት እንዳባባሰውና በቂ እርዳታም እንዳልደረሳቸው አመልክተዋል።

በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከ140 ሺህ በላይ ሰው በአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው የወረዳው አስተዳዳሪ አስታውቀዋል።

ደርቁን አስመልክቶ ከደቡብ ክልል ምክር ቤት ጋር መወያየታቸውን ለክልሉ መንግሥት ቴሌቪዥን የገለፁት የክልሉ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ጋንታ ጋምአ በክልሉ ውስጥ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሰው የምግብ እጥረት እንዳጋጠመው ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ፡፡

XS
SM
MD
LG