በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቻይና ህዝብ ብዛት ከ60 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀነሰ


ፎቶ ፋይል፦ መንገደኞች በባቡር ለመሳፈር ስልፍ ይዘው፣ ደቡብ ቻይና ጓንግዶንግ ግዛት ሼንዘን የሚገኘው ባቡር ጣቢያ፡፡
ፎቶ ፋይል፦ መንገደኞች በባቡር ለመሳፈር ስልፍ ይዘው፣ ደቡብ ቻይና ጓንግዶንግ ግዛት ሼንዘን የሚገኘው ባቡር ጣቢያ፡፡

ቻይና የህዝቧ ብዛት ከስድሳ ዓመታት በኋላ እአአ ባለፈው 2022 ለመጀመሪያ ጊዜ መቀነሱን አስታወቀች።

የሀገሪቱ የስታቲስታቲክስ ቢሮ ባወጣው መረጃ መሰረት ባለፈው 2022 ዓመተ ምህረት 9 ነጥብ 56 ህጻናት የተወለዱ ሲሆን 10 ነጥብ 41 ሰዎች ሞተዋል። በዚያም ሂሳብ የህዝቡ ብዛት በ850 ሺህ ቀንሷል።

እአአ በ1950ዎቹ ዓመታት የማኦ ሴ ዶንግ የፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ፖሊሲ ሳቢያ በሚሊዮኖች የተቆጠሩ ዜጎች በረሃብ ካለቀ ወዲህ የህዝቧ ብዛት ሲቀንስ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ተመልክቷል።

XS
SM
MD
LG