በሁለተኛ ቀን የኢትዮጵያ ቆይታቸው ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ጋራ የተወያዩት አዲሱ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋንግ፣ በሀገራቸው ድጋፍ የተገነባውን የአፍሪካ በሽታዎች መቆጣጠርና መከላከል ማዕከልም መርቀው ከፍተዋል።
በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር አፍሪካ ሀያላን ሀገሮች የሚተባበሩባት እንጂ ውድድር የሚያደርጉባት ሜዳ መሆን የለባትም ያሉት ሚኒስትሩ፣ አሕጉሪቱ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት እንደሚገባም ገልፀዋል።
/ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/