በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የክሬሚያው ገዥ የዩክሬን ድሮን ተመቶ መውደቁን ተናገሩ


የሩሲያና የዩክሬን ጦርነት 316ኛ ቀኑን ሲይዝ በዶኔትስክ ግዛት ባክሙት በሚገኘው የሰብአዊ እርዳታ ጣቢያ የአካባቢው ሰዎች የገና በዓል ዋዜማን ለማክበር ተሰብስበዋል ታህሳስ 28/2015
የሩሲያና የዩክሬን ጦርነት 316ኛ ቀኑን ሲይዝ በዶኔትስክ ግዛት ባክሙት በሚገኘው የሰብአዊ እርዳታ ጣቢያ የአካባቢው ሰዎች የገና በዓል ዋዜማን ለማክበር ተሰብስበዋል ታህሳስ 28/2015

በሩሲያ የሚደገፉ የክሬሚያዋ ሴቫስቶፖል ከተማ አገረ ገዥ ሚካኤል ራዛቮዜቭ ከዩክሬን የተላከ ነው ያሉት አንድ ሰው አልባ ድሮን አውሮፕላን የኦርቶዶክሱ የገና በዓል በሚከበርበት ዛሬ ቅዳሜ ተመቶ መወደቁን አስታወቁ።

ራዛቮዜቭ “ እነዚህ ሰብአዊነት የጎደላቸው ሰዎች በተቀደሰው የገና በዓል እንኳ ጀግናዋን ከተማችንን ከማጥቃት ሙከራቸው አልታቀቡም” ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ሩሲያ ክሬሚያን ከዩክሬን በመንጠቅ ወደ ራሷ ግዛት የቀላቀለችው እኤአ በ20144 መሆኑ ተዘግቧል።

ዩክሬን ሩሲያ ዩክሬንን ከመውረሯ በፊት ወደ ግዛቷ የቀላቀለቻቸውንና ከወረራውም በኋላ የያዘቻቸውን ግዛቶችዋን እንደምታስለቀቅ አስታውቃለች።

ሴባስቶፖል ሩሲያ በጥቁር ባህል የምታንቀሳቅሳቸው የባህር ትራንስፖርቶችዋ መናኻሪያ መሆናዋ ተመልክቷል።

በተያይዘ ዜናም የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የገናን በዐል ዋዜማ ሌሊቱን ክሬምሊን ውስጥ በሚገኘው ካቴድራል ማክበራቸው ተነገሯል።

ፑቲን ለሩሲያው ኦሮቶዶክስ የገና በዓል 36 ሰዐት የሚቆይ የተኩስ ማቆም ያወጁ ቢሆንም ውጊያው ግን እየቀጠለ መሆኑን የብሪታኒያው መከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።

XS
SM
MD
LG