በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በደቡብ አፍሪካ የነዳጅ ቦቴ ፍንዳታ የሞቱት ሠዎች ቁጥር 27 ደረሰ


በደቡብ አፍሪካ ጁሃንስበርግ አቅራቢያ በፈነዳው የነዳጅ ቦቴ ፍንዳታ በተጎዳው ድልድይ መግቢያ ላይ የተቃጠለውን የጭነት መኪና ሰዎች ቆመው ሲመለከቱ - ታህሳስ 24፣ 2022
በደቡብ አፍሪካ ጁሃንስበርግ አቅራቢያ በፈነዳው የነዳጅ ቦቴ ፍንዳታ በተጎዳው ድልድይ መግቢያ ላይ የተቃጠለውን የጭነት መኪና ሰዎች ቆመው ሲመለከቱ - ታህሳስ 24፣ 2022

በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ በፈረንጆች ገና ዋዜማ በደረሰው የነዳጅ ቦቴ ፍንዳታ የሞቱት ሠዎች ቁጥር 27 መድረሱን የከተማው ጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

የቦቴው ፍንዳታ የታምቦ መታሰቢያ ሆስፒታል የድንገተኛ ክፍልን ጣሪያ ሲገነጥል፣ ሁለት ቤቶችን ሙሉ ለሙሉ አውድሟል፣ በርካታ ቤቶችን ደግሞ አፍርሷል። እስከ 1600 ጫማ ርቀት ላይ የነበሩ ሰዎችንም ጎድቷል።

የከተማው ጤና ባለሥልጣን እንዳስታውቀው ከሟቾቹ ውስጥ 10 የሚሆኑት የሆስፒታሉ ሰራተኞች ናቸው።

እንደ ሮይተርስ ዜና ወኪል ዘገባ ከሆነ፣ በመጀመሪያ 18 ሰዎች በፍንዳታው እንደሞቱ ባለሥልጣናት ቢያስታውቁም፣ ፍንዳታው በሰዎች ላይ በፈጠረው ከፍተኛ ቃጠሎ ምክንያት የሟቾቹ ቁጥር ጨምሯል።

የቦቴው ሹፌር በግድያ ተጠርጥሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ በቂ ማስረጃ አልተገኘበትም በሚል ትናንት ተለቋል ሲሉ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

XS
SM
MD
LG