በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢራን 2 የባሃይ ዕምነት መሪዎች እንደገና የ10 ዐመት እስራት ተፈረደባቸው


ፋይል - እ.አ.አ ሰኔ 19 2011 በሪዮ ዴጄኔሮ ኮፓባባና የባህር ዳርቻ በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በኢራን የታሰሩ የባሃይ የሃይማኖት መሪዎች በርካታ ምስሎች ታይተዋል።
ፋይል - እ.አ.አ ሰኔ 19 2011 በሪዮ ዴጄኔሮ ኮፓባባና የባህር ዳርቻ በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በኢራን የታሰሩ የባሃይ የሃይማኖት መሪዎች በርካታ ምስሎች ታይተዋል።

የኢራን መንግሥት በሀገሪቱ እስልምና ካልሆኑ ዕምነቶች ውስጥ ትልቁ በሆነው የባሃይ እምነት ላይ በቀጠለው አፈና ሁለቱን መሪዎች ማሰሩን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የማህበረሰቡ ተወካዮች ትናንት ዕሁድ አስታውቀዋል።

የስድሳ ዘጠኝ ዐመቷ ማህቫዥ ሳቤት እና የስድሳ አመቷ ፋሪባ ካማላባዲ ካህን ቀደም በባሃዮች ትግል አንቂነታቸው የተነሳ ሁለቱም ለአስር ዐመታት ታስረው የነበሩ ሲሆን በቅርቡ አንድ ሰዐት በፈጀ የፍርድ ሂደት አዲስ የአስር አመት እስራት እንደተፈረደባቸው ገልጸዋል። ሁለቱ ሴቶች የታሰሩት ባለፈው ሃምሌ ወር መሆኑን የባሃዮች አለም አቀፍ ማህበረሰብ አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG