በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢትዮጵያው ግጭት አሁናዊ ሁኔታዎች


በኢትዮጵያው ግጭት አሁናዊ ሁኔታዎች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:27 0:00

በኢትዮጵያው ግጭት አሁናዊ ሁኔታዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር የሰሜን ኢትዮጵያውን ግጭት በሠላም መፍታት በሚቻልበት ጉዳይ አዲስ አበባ ላይ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተወያዩ፡፡

በሌላ ዜና፣ ጦርነቱ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ አቅጣጫዎች ተባብሶ ቀጥሏል ሲሉ የህወሓቱ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ለክልሉ መገናኛ ብዙኃን ተናገሩ፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ ስለጦርነቱ ምንም አይነት መግለጫም ይሁን ምላሽ ከመስጠት እንደተቆጠበ ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ “አየርላንድ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ከሚጻረሩ ድርጊቶቿ ልትታቀብ ይገባል” ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አሳሰበ፡፡

ይህ ካልሆነ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታችንን አስፈላጊነት እናጤለን ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለአየርላንድ መንግሥት በጻፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡

ለደብዳቤው እስካሁን ከአየርላንድ በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም፡፡

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]

XS
SM
MD
LG