በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ተፈናቃዮች አሁንም ዕርዳታ እየጠበቁ ነው


የኢትዮጵያ ካርታ
የኢትዮጵያ ካርታ

እስካሁን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳልተደረገላቸው ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 25 በተፈፀመው ጥቃት ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፣ አሙሩ ወረዳ የተፈናቀሉ ዜጎች ተናግረዋል ።

በታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት ምክንያት ከአጋምሳ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች የተፈናቀሉት እነዚህ ዜጎች በትምህርት ቤቶች እና በዕምነት ተቋማት ተጠልለው እንደሚገኙም ነው የገለፁት።

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የአደጋ ስጋት ቅነሳ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በበኩሉ የተፈናቀሉ ሰዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የተዋቀረ ኮሚቴ ወደ አካባቢው ማምራቱን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጷጉሜ 1/2014 ባወጣው መግለጫ ከ20 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን ገልጾ፣ በአፋጣኝ ዕርዳታ እንዲደረግላቸውም አሳስቦ ነበር።

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ተፈናቃዮች አሁንም ዕርዳታ እየጠበቁ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:07 0:00

XS
SM
MD
LG