በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ተፈናቃዮች አሁንም ዕርዳታ እየጠበቁ ነው


የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ተፈናቃዮች አሁንም ዕርዳታ እየጠበቁ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:07 0:00

እስካሁን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳልተደረገላቸው ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 25 በተፈፀመው ጥቃት ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፣ አሙሩ ወረዳ የተፈናቀሉ ዜጎች ተናግረዋል ።

በታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት ምክንያት ከአጋምሳ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች የተፈናቀሉት እነዚህ ዜጎች በትምህርት ቤቶች እና በዕምነት ተቋማት ተጠልለው እንደሚገኙም ነው የገለፁት።

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የአደጋ ስጋት ቅነሳ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በበኩሉ የተፈናቀሉ ሰዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የተዋቀረ ኮሚቴ ወደ አካባቢው ማምራቱን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጷጉሜ 1/2014 ባወጣው መግለጫ ከ20 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን ገልጾ፣ በአፋጣኝ ዕርዳታ እንዲደረግላቸውም አሳስቦ ነበር።

XS
SM
MD
LG