በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሱዳን:- ጎርፍ 66 ሰው ገደለ


ፎቶ ፋይል፦ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የፈራረሱ መኖሪያ ቤቶች ከሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በ20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አልካድሮ ከተማ እአአ 8/2020
ፎቶ ፋይል፦ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የፈራረሱ መኖሪያ ቤቶች ከሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በ20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አልካድሮ ከተማ እአአ 8/2020

ሱዳን ውስጥ እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሞተው ሰው ቁጥር 66 መድረሱን አንድ የሃገሪቱ ባለሥልጣን አስታወቁ።

ሌሎች ቢያንስ 28 ሰዎች በጎርፉ መጎዳታቸውን የሱዳን የዜጎች ደኅንነት ጥበቃ ብሄራዊ ምክር ቤት ባለሥልጣን ገልጠዋል።

ሃያ አራት ሺህ መኖሪያ ቤቶችና ሁለት የመንግሥት መሥሪያ ቤት ህንፃዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ወይም ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ባለሥልጣኑ አመልክተዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ደግሞ 238 የጤና ተቋማት መጥለቅለቃቸውን አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG