በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ወደ ዳባት ካምፕ የተወሰዱ ኤርትራውያን ችግር ላይ መሆናቸውን ተናገሩ


ወደ ዳባት ካምፕ የተወሰዱ ኤርትራውያን ችግር ላይ መሆናቸውን ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:44 0:00

ወደ ዳባት ካምፕ የተወሰዱ ኤርትራውያን ችግር ላይ መሆናቸውን ተናገሩ

የዛሬ አስር ቀን ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ የሚገኝ ቤተክርስቲያን ተሳልመው ሲመለሱ ለገጣፎ አካባቢ በፖሊስ የተያዙትና በግድ ታፍሰው ወደ ዳባት ካምፕ የተወሰዱት ኤርትራውያን “እስካሁን ድረስ ቀለብ ስላልተሰጠን፣ በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንገኛለን” ሲሉ አስታውቀዋል።

ታፍሰው ከተወሰዱት ሰዎች መካከል የሚያጠቡ እናቶች፣ በመድሐኒት የሚኖሩ ህመምተኞች እና የአዕምሮ ችግር ያለባቸው ሰዎች እንደሚገኙበት ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ ሰዎች ገልፀዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ከኢትዮጵያ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት እንዲሁም ከፌዴራል ፖሊስ የተገኘ ምላሽና አስተያየት ባይኖርም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ግን ጉዳዩን እየተከታተለ መሆኑን አስታውቋል።

/ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

XS
SM
MD
LG