ጉዳያቸው በችሎት እየታየ ያለ የኦሮምያ ኒውስ ኔትዎርክ ጋዜጠኞች በዳኞች ነፃነት ላይ ጥያቄ አንስተው እንዲቀየሩላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ የኦሮምያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሳይቀበለው ቀርቷል።
ለዛሬ ተቀጥሮ በነበረው በነ ቃስም አብዱላሂ ስም በተከፈተ ዶሴ ተከስሰው ጉዳያቸው እየታየ ባሉት ሁለት የኦሮምያ ኒውስ ኔትዎርክና ሌሎች 15 ሰዎች ጉዳይ ላይ የኦሮምያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ውሳኔ ሰጥቷል።
ተከሳሾቹ ባለፈው ቀጠሯቸው በዳኞች ላይ ያቀረቡትን አቤቱታ ችሎቱ መርምሮ ውድቅ ማድረጉን የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ ቶለማርያም ገመዳ ለቪኦኤ ገልፀዋል።
ዝርዝሩን ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።