አጋሩ
Print
በደቡብ አፍሪካ መጠጥ ቤት ውስጥ በትንሹ 20 የሚሆኑ ወጣቶች ሞቱ። የወጣቶቹ አሟሟት ምክንያት አለመታወቁን ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የምስራቃዊ ኬፕ ታውን ግዛት የጤና ክፍል ቃል አቀባይ ሲያንዳ ማናና የሟቾቹ አስክሬን በአቅራቢያ ወደሚገኝ የአስክሬን ማቆያ መጓጓዙን እና በዛ ምርመራ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
ሮይተርስ ሟቾቹ እድሜያቸው ከ18 እስከ 20 ያሉ ወጣቶች መሆናቸውን ዘግቧል።