በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከ9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ እህል እንዳልተሰበሰበ እና እንዳልተመረተ አማራ ክልል ገለፀ


ከ9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ እህል እንዳልተሰበሰበ እና እንዳልተመረተ አማራ ክልል ገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:06 0:00

ከ9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ እህል እንዳልተሰበሰበ እና እንዳልተመረተ አማራ ክልል ገለፀ

በሰሜን ኢትዮጵያ ያለፈው ዓመት የምርት ወቅት ቢባክንባቸውም ለዘንድሮው ግን እየተዘጋጁ እንደሆነ ጦርነት በተካሄደባቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች የሚገኙ አርሶ አደሮች ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት ባለማምረታቸው እና ያመረቱትን ምርትም በጦርነቱ ምክንያት ባለመሰብሰባቸው የተፈጠረውን ክፍተት በቴክኖሎጂ ታግዘዉ ለመሙላት እንደሚሠሩም አርሶ አደሮቹ ገልፀዋል።

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ እንዳለው በጦርነቱ ምክንያት ከ9 ሚሊዮን ኩንታል በላይ እህል አልተመረተም፣ አልተሰበሰበም ወይም ተዘርፏል።

ጦርነቱ በምርት መጠን ላይ ያደረሰው ጉዳት ከባድ ቢሆንም ግብርናውን በማዘመን የተሻለ ነገር ለመሥራት መታቀዱን የክልሉ መንግሥት 136 የእርሻ ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች ባስረከበበት ሥነ ስርዓት ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ተናግረዋል።

ዘገባው የአስቴር ምስጋናው ነው።

XS
SM
MD
LG