በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ጀነራል ተፈራ ማሞ እስካሁን የት እንዳሉ ማወቅ አለመቻላቸውን ባለቤታቸውና የግል ጠባቂያቸው ተናገሩ


ጀነራል ተፈራ ማሞ እስካሁን የት እንዳሉ ማወቅ አለመቻላቸውን ባለቤታቸውና የግል ጠባቂያቸው ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:48 0:00

ጀነራል ተፈራ ማሞ እስካሁን የት እንዳሉ ማወቅ አለመቻላቸውን ባለቤታቸውና የግል ጠባቂያቸው ተናገሩ

የቀድሞው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ጀነራል ተፈራ ማሞ ትናንት እረፋዱ ላይ ሰው ለማግኘት አዲስ አበባ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መውጣታቸውን የሚናገሩት ባለቤታቸው ወ/ሮ መነን ኃይለማሪያም፤ ከቀኑ 10 ሰዓት በኋላ በእጅ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ቢደውሉም እንደማይነሳና ዛሬም ወደ ተለያዩ የፍትህ ተቋማት ቢሄዱም ምላሽ አለማግኘታቸውን ተናግረዋል።

"ትናንት ረፋዱ ላይ ከአቶ ዩሐንስ ቧያለው ጋር ቀጠሮ እንዳለውና እርሱን ለማግኘት እንደሚሄድ ነግሮኝ ነበር ከቤት የወጣው” ያሉት ወ/ሮ መነን “ሁሌ ስብሰባ ወይም ሌላ ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ ጉዳይ ሲኖረው ስልክ ደውሎ ወይም በአጭር የጽሑፍ መልዕክት ያለበትን ሁኔታ ያሳውቅ ነበት ትናንት ግን ይህን አላደረገም። ሁኔታው አላምር ሲለኝ ስልኬን አንስቼ ደጋግሜ ደወልኩ ስልኩ አይነሳም አቶ ዩሀንስ ጋር ደወልኩ እስከ 10:30 ድረስ አብረው እንደነበሩና ወደ መኪናው አስገብቶት እንደተለያዩ ነገረኝ ማታም የቅርብ ዘመዶቻችን ጋር ስደዋውል አየሁት የሚል ሰው አላገኘሁም" ብለዋል።

ዛሬ ጠዋት ፌዴራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ቢሄዱም ሊያገኟቸው እንዳልቻሉና በኋላም ወደ ብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ ሲሄዱ በነገው ዕለት ወረቀት ጽፈው ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ እንደተነገራቸው ገልፀዋል።

ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ

XS
SM
MD
LG