በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አፋር እና አማራን ክልል በሚያጎራብት ቦታ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ


አፋር እና አማራን ክልል በሚያጎራብት ቦታ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:52 0:00

አፋር እና አማራን ክልል በሚያጎራብት ቦታ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ

በአፋር ክልል ዞን አንድና በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አጎራባች አካባቢዎች የሚከሰተውን የጸጥታ ችግር በመቅረፍ እና በችግሩ ምክንያት የተዘረፉ ንብረቶችን በማስመለስ ሂደት ላይ በነበሩ የሁለቱም ወገን አመራሮች ላይ ለጊዜው ማንንታቸው አልታወቀም የተባሉ ታጣቂዎች በሰነዘሩት ጥቃት ከአራት የማያንሱ ሰዎች መሞታቸውን እና ወደ ዐስር የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው ተገለጸ፡፡

ከኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ወሰንተኛ የሆነው የአፋር ክልሉ አድአር ወረዳ ድርጊቱ ሁለቱንም ወገኖች ለማጥፋት ሆን ተብሎ የታቀደ ነበር ሲል አስታውቋል፡፡

ድርጊቱን የፈጸሙት አካላት ለጊዜው ማምለጣቸው ተሰምቷል፡፡

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳዳር ዞን ጥቃቱ ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ እለት የተፈጸመ ሲሆን ግጭቱ የብሔር መልክ እንዳይዝ በተደረገው ጥንቃቄ አሁን አካባቢዎቹ በአንጻራዊ ሰላም ይገኛሉ ነው ብሏል።

ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ

XS
SM
MD
LG