በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት ከዩክሬንን ፕሬዚደንት ጋር ተነጋገሩ


የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ፣ ከዩክሬንን ፕሬዚደንት ቭሎድሜር ዘለንስኪ ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል ።
የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ፣ ከዩክሬንን ፕሬዚደንት ቭሎድሜር ዘለንስኪ ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል ።

የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ፣ እና አራት ዴሞክራት የኮንግረስ አባላት የዩክሬንን መናገሻ ከተማ ኪቭን ቅዳሜ ዕለት ጎብኝተዋል ።ከዩክሬንን ፕሬዚደንት ቭሎድሜር ዘለንስኪ ጋር ተገናኝተውም ተነገራርዋል ።

ጉብኝቱ ዩክሬንን ለነጻነት ስለምታደርገው ፍልሚያ ለማመስገን፣ ፍልሚያው እስኪጠናቀቅ ዩናይትድ ስቴትስ ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ፔሎሲ ለዘለንሲክ ነግረዋቸዋል ።

ከፔሎሲ ጋር ወደ ዩክሬን ያቀኑት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች - የካሊፎርኒያው አዳም ሼፍ፣ የማሳቹሴቱ ጂም ማክገቨርን ፣ የኒዮርኩ ግሪጎሪ ሚክስ እና የኮሎራዶው ጄሰን ክሮ ናቸው ።

ይህ በእንዲህ እያለ ቅዳሜ ዕለት በኦዴሳ የአየር ማረፊያ ላይ በደረሰ የሩሲያ የሚሳኤል ጥቃት የአየር ማኮብኮቢያው ጎዳና መውደሙን የዩክሬን ጦር ይፋ አድርጓል ።

ለሲኤን ኤን ኤን ምስክርነቷን የሰጠች አንድ ግለሰብ ፣በደቡባዊቷ ከተማ ሰማይ ላይ ቢያንስ አንድ ተዋጊ አውሮፕላን መመልከቷን ፣ የአደጋ ጊዜ ደዋል ከተሰማ በኃላ መላ ከተማዋ በፍንደታ መናጧን ተናግራለች ።

ሩሲያ የዩክሬንን ምስራቃዊ የዶንባስ ቀጠና ብትደበድብም ሶስት ያነጣጠረችባቸውን ስፍራዎች ማለትም ፣ ሊማን፣ ሲቨርዶንቴስክ እና ፖፕሳናን ለመቆጣጠር እንደተሳናት የዩክሬን ጦር አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG