በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጀርመን መከላከያ ሚኒስቴር ጦራቸው በማሊ የሚኖረው ቆይታ አጠራጣሪ ነው አሉ 


የጀርመን መከላከያ ሚንስትር ክሪስቲን ላምብሬክት ሚያዚያ 6, 2022 በርሊን በሚገኘው ፓርላማ ንግግር ሲያደርጉ
የጀርመን መከላከያ ሚንስትር ክሪስቲን ላምብሬክት ሚያዚያ 6, 2022 በርሊን በሚገኘው ፓርላማ ንግግር ሲያደርጉ

የጀርመን የመከላከያ ሚንስትር ማሊ ሞራ ውስጥ ከተፈጸመው የጭካኔ አድራጎት በኋላ የጀርመን የጦር ኅይል ማሊ የመቆየቱ ጉዳይ እንደሚያጠራጥራቸው በድጋሚ አስታወቁ።

ሚንስትር ክሪስቲን ላምብሬክት ይህን ያስታወቁት በትናንቱ የማሊ ጉብኝታቸው ባደረጉት ንግግር ሞራ መንደር ውስጥ የደረሰውን አንስተው ሲናገሩ ነው።

የማሊ መንግሥት ሞራ ውስጥ 203 ሽብርተኞችን ደምሥሰናል ቢልም የዜና ተቋማት እና ሂዩማን ራይትስ ዋች ያነጋገሯቸው የዐይን ምስክሮች ግን የመንግስት ወታደሮች ብዛት ያላቸው ሰላማዊ ሰዎችን እንደገደሉ ገልጸዋል።

ላምብሬኽት ሰሜን ጋዎ የሚገኙ የጀርመን ወታደሮችን ካነጋገሩ በኋላ እንዲህ ላለ አገዛዝ ድጋፍ መስጠት እንፈልጋለን ወይ ? የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን ከሚኒስቴራቸው የወጣ መረጃ አመልክቷል።

"እጅግ የላቀ ብቃት ያላቸው የጀርመን ወታደሮች የሚያሰለጥኗቸው የማሊ ወታደሮች ይህን ብቃታቸውን ይዘው - ከሩስያ ኃይሎች ቅጥረኛ ወታደሮች ጋር ይሰማራሉ - ያሉት የጀርመን የመከላክያ ሚንስትር ላምብሬኽት - በተለይም ሞራ ላይ ከተፈጸመው ተግባር በኋላ ከእኛ እሴቶች ጋር ይጣጣማል ወይ የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ ነው" ማለታቸው ተዘግቧል።

XS
SM
MD
LG