ለዩክሬይን ኃይሎች ተጨማሪ የጦር መሣሪያ እየተላከላቸው መሆኑን የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን አስታውቀዋል።
የሰሜን አትላንቲክ የጦር ትብብር ድርጅት “ኔቶ” እና የባለጠጎቹ የቡድን ሰባት አባል ሀገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ብራስልስ ላይ ያካሄዱትን ስብሰባ ሲያጠናቅቁ ብሊንከን በሰጡት ቃል "ሁኔታው አጣዳፊ በመሆኑ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶታል" ብለዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የዩክሬይን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሮ ኩሌባ ሲናገሩ “ከወራሪው የሩሲያ ኃይል ጋር የሚካሄደው ቀጣዩ ፍልሚያ ሁለተኛው የዓለም ጦርነትን የሚመስል ይሆናል" ሲሉ ኔቶን አሳስበዋል።