በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የካማላ ሃሪስ ባለቤት ለኮሮናቫይረስ መጋለጣቸው ተገለጸ


ፎቶ ፋይል፦ የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስ እና ባለቤታቸው ዳግላስ ኤምሆፍ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ፕሬዚዳንታዊ በዓለ ሲመት ዕለት በእግራቸው ሲጓዙ በዋሽንግተን እአአ ጥር 20/2021
ፎቶ ፋይል፦ የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስ እና ባለቤታቸው ዳግላስ ኤምሆፍ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ፕሬዚዳንታዊ በዓለ ሲመት ዕለት በእግራቸው ሲጓዙ በዋሽንግተን እአአ ጥር 20/2021

የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስ ባለቤት ደግ ኢምሆፍ ኮሮናቫይረስ እንደያዛቸው በምርመራ መታወቁን ዋይት ኃውስ አስታወቀ። ባለቤታቸው ምክትል ፕሬዚዳንት ሃሪስ ተመርምረው ከቫይረሱ ነጻ ሲሆኑ ሆኖም በባለቤታቸው መጋለጥ የተነሳ የሥራ መርኃ ግብሮቻቸውን ቀንሰዋል።

ሃሪስ በትዊተር ባወጡት ቃል "ደግ ደህና ነው፥ ክትባቶቻችንን ከነማጠናከሪያው መውሰዳችን ጥሩ ነው" ብለዋል።

ምክትል ፕሬዚዳንቷ ትናንት ማታ በዋይት ኃውስ በተካሄደው የእኩል ክፍያ ጉዳይን የተመለከተ ዝግጅት ላይ አልተገኙም ሆኖም ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እንዲህ ብለዋል።

"በቡድናችን እኮራለሁ። በተለይም ደግሞ ዛሬ በዚህ ዝግጅት ሊያቀርቡኝ በነበሩት በካማላ ሃሪስ እኮራለሁ። ባለቤታቸው ለቫይረሱ መጋለጣቸውን ተከትሎ ምንም እንኳን እንደተነገረኝ ባለቤታቸው በጣም ጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ ቢሆኑም ለጥንቃቄ ሲሉ አለመምጣቱን መርጠዋል፣ ለጥንቃቄ ሲሉ ነው ያልመጡት” ብለዋል።

ምክትል ፕሬዚዳንት ሃሪስ ትናንት ከሰዓት በኋላ ከፕሬዚዳንት ባይደን ጋር የነበሩ ሲሆን የአንድ ነጥብ አምስት ትሪሊዮን ዶላር የመንግሥት በጀት በተፈረመበት ስነ ስርዐት ላይ ከምክር ቤት አባላት ጋር ተገናኝተዋል።

XS
SM
MD
LG