በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሰላማዊ ሰዎችን የገደሉና ያቃጠሉ ማንነታቸው ተለይቶ ተጠያቂ እንዲሆኑ ኢሰመኮ ጠየቀ


አቶ ይበቃል ግዛው
አቶ ይበቃል ግዛው

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተጠርጣሪዎችን ከዳኝነት ውጪ መግደላቸውንና አስክሬናቸውን ማቃጠላቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ማረጋገጡን አስታወቀ።

ለዚህ ድርጊት መንስኤ የሆነው ታጥቂዎች በመንግሥት ኃይሎችና ሰላማዊ ሰዎች ላይ የፈፀሙትን ግድያም ማረጋገጡን ገልጿል። የኮሚሽኑ የክትትልና የምርመራ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ይበቃል ግዛው ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፀጥታ ኃይሎች በተጨማሪ ሲቪሎች በድርጊቱ ተሳታፊ እንደነበሩ በቪዲዮው ላይ መታየቱን ገልፀዋል።

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ድርጊቱ እንዳስደነገጠው አስታውቆ ጉዳዩ ተጣርቶ ለሕግ እንዲቀርብ አሳስቧል።

በውጭ ሀገሮች “በትግራይ ክልል መንግሥት ስም” እንደሚንቀሳቀስ የሚናገረው ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ዮሃንስ አብርሃ ስለተፈፀመው ድርጊት በመንግሥትም በኮሚሽኑም ላይ ክስና ወቀሳ አሰምተዋል።

ሰላማዊ ሰዎችን የገደሉና ያቃጠሉ ማንነታቸው ተለይቶ ተጠያቂ እንዲሆኑ ኢሰመኮ ጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:16 0:00

XS
SM
MD
LG