አዲስ አበባ —
በእነ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል መዝገብ ስር ካሉ ተከሳሾች መካከል ስድስት ግለሰቦች ክሳቸው የተነሳላቸው በሰብዓዊነት መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በሰጡት መግለጫ፣ በመዝገቡ የሚገኙ ሌሎች ተከሳሾች የክስ ሂደት እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ በአቶ ጀዋር መሐመድና አቶ እስክንድር ነጋ መዝገብ የተከሰሱት ደግሞ ክሳቸው መቋረጡን በመጥቀስ ይህም ለሀገራዊ ምክክሩ ውጤታማነት ተብሎ የተወሰነ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
/ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ/