በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ የተመድ መርማሪዎችን እንድትቀበል የሚያስገድድ ዓለም አቀፍ ህግ አለን?


.
.

ኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጽመዋል የተባሉ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎችን ለመመርመር የሚችል የባለሙያዎች ቡድን ለማቋቋም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ከሰሞኑ ወስኗል ።

ድርጅቱ ኢትዮጵያን በሚመለከት የተለያዩ ሪፖርቶችን ሲያቀርብ ነበር። ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር በመሆን ከጥቂት ሳምንታት በፊት የምርምራ ውጤታቸውን ቀደም ብለው ይፋ ማድረጋቸው ይታዋሳል ። ይሁንና የአሁኑ ውሳኔ የውዝግብ ምንጭ ሆኗል ።ለምን ?

ለዚህ መልስ ለማግኘት ሀብታሙ ስዩም አመሸሹን ወደ ዶክተር አደም ካሴ ደውሏል። ዶ/ር አደም በተለያዩ ዓለም አቀፍ የአውታሮች ላይ ከሚያቀርቧቸው በተለይ አፍሪካን የሚመለከቱ ህግ እና ፖለቲካን ከሚመለከቱ ትንታኔዎች በተጨማሪ ኔዘርላንድስ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የዴሞክራሲ እና የምርጫ ድጋፍ ኢንስቲትዮት ባልደረባ ናቸው።

ሙሉ መሰናዶውን ከስር ቀርቧል ።

ኢትዮጵያ የተመድ መርማሪዎችን እንድትቀበል የሚያስገድድ ዓለም አቀፍ ህግ አለን ?
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:54 0:00

XS
SM
MD
LG