ዋሽንግተን ዲሲ —
ኢትዮጵያዊው የምስል ዘጋቢ ሶለን ገመቹ ትልቅ ክብር የሚሰጠው ሮሪ ፔክ ሽልማትን ከሰሞኑ ተቀብሏል። በ1990ዎቹ የጎረጎሳዊያኑ ዘመን ሩሲያ ውስጥ በስራ ላይ እያለ በተገደለው ጋዜጠኛ ሮሪ ፔክ ስም የተሰየመው ሽልማት ፣ በመላ ዓለም የላቀ ስራ ላሳዩ “ፍሪላንስ” ጋዜጠኞች የሚሰጥ ሽልማት ነው ።
ሀብታሙ ስዩም ላለፉት 7 አመታት ለአሶሼትድ ፕረስ በምስል ዘጋቢነት ከሰራው ሶለን ገመቹ ጋር ለሽልማት ስለበቃው ስራ እና ተያያዥ ጉዳዮች ተወያይቷል ። በተለይ በቴሌቭዥን እና ማህበራዊ መገናኛዎች የምትመለከቱን አድማጮች መሰናዶው የታጀበባቸው አንዳንድ ምስሎች የአሰቃቂነት ይዘት እንዳላቸው አስቀድመን ለመጠቆም እንወዳለን ።
የሀብታሙና የሶለን ቆይታ እነሆ።