በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኦባሳንጆ ወደ መቀሌ የተጓዙት እውነትን ለማፈላለግ መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ


ኦባሳንጆ ወደ መቀሌ የተጓዙት እውነትን ለማፈላለግ መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:11 0:00

የኢትዮጵያ ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒሰትር ዲኤታ ሠላማዊት ካሣ

የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛና የቀድሞው የናይጀሪያ ኘሬዚዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ወደ መቀሌ ተጉዘው ከህወሃት መሪዎች ጋር መወያየታቸውን ኅብረቱ አስታውቋል ።

ልዩ ልዑኩ ከህወሃት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ጋር ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጌታቸዉ ረዳ በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥትም በበኩሉ ኦባሳንጆ ወደ መቀሌ መጓዛቸውን አረጋግጧል።

ጉዟቸውም እውነትን የማፈላለግና መረጃዎችን ከሁሉም አካል የመሰብሰብ ተልእኮ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒሰትር ዲኤታ ሠላማዊት ካሣ ለአሜሪካ ድምፅ አስረድተዋል።

"በመንግሥት በኩል የሚደበቅ ምንም ነገር የለም" ያሉት ሚኒስትር ዲኤታዋ፤ ማናገር አለብኝ ብለው የሚያስቧቸውን አካላት እንዲያናግሩ ሁኔታው መመቻቸቱን ገልፀዋል።

XS
SM
MD
LG