በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ ምርጫ የመጨረሻ ዝግጅቶች


ሶሊያና ሽመልስ
ሶሊያና ሽመልስ

ልክ የዛሬ ሳምንት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ከዚህ ምሽት ጀምሮ ወደተለያዩ አካባቢዎች እንደሚላኩ የጠቀሱት የቦርዱ የኮምዩኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ የማበረታታት ስራ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።

45 ሺህ የሚሆኑ የአገር ውስጥ ታዛቢዎችም ፈቃድ ወይም ባጅ መውሰዳቸውን አስረድተዋል።

በፀጥታ እና በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው የዛሬ ሳምንት በማይካሄድባቸው 59 የምርጫ ክልሎች ደግሞ ጷግሜ 1 ቀን እንደሚካሄድ የኮምዩኒኬሽን አማካሪዋ አስታውቀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

የኢትዮጵያ ምርጫ የመጨረሻ ዝግጅቶች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:03 0:00


XS
SM
MD
LG