ዋሺንግተን ዲሲ —
በእንግሊዝኛ ኦቲዝም ተብሎ ለሚጠራው የአእምሮ ሥራ ሂደት መዛባት ችግር ተጋላጭ ለሆኑ ልጆች ተሟጋችነታቸው እና ባደረጉትም ድጋፍ እጅግ ታዋቂ የሆኑት ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮቪድ-19 ሳቢያ በዛሬው ዕለት ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቧል።
የጆይ ኦቲዝም ማዕከል እንዲሁም የኒያ ፋውንዴሽን መስራች እና ሥራ አስኪያጅዋ ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በአዲስ አበባ ሚሊኒየም የኮቪድ-19 ጽኑ ህክምና ማዕከል ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ማረፋቸው ታውቋል።
ወ/ሮ ዘኒ የአዕምሮ ዕድገት ዝግመት እክል ተጋላጭ ከሆነው ወንድ ልጃቸውን በመንከባከብ ባገኙት ዕውቀት እና ተመክሮ ህብረተሰቡም በጥልቀት ግንዛቤ እንዲኖረው እና ለተመሳሳይ ችግር የተጋለጡ ሌሎች ልጆችም ድጋፍ እንዲያገኙ ለአያሌ ዓመታት በትጋት ሲሰሩ ኖረዋል።