በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ዘጋች


ፎቶ ፋይል ፤ ትዮጵያን በሰሜን ምዕራብ በኩል ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ድንበር ሰዎች ሲተላለፉ እ.ኤ.አ ሰኔ 3/2015 ዓ.ም የተነሳ።/ፎቶ- ኤፒ ሙሉ ጌታ አያና
ፎቶ ፋይል ፤ ትዮጵያን በሰሜን ምዕራብ በኩል ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ድንበር ሰዎች ሲተላለፉ እ.ኤ.አ ሰኔ 3/2015 ዓ.ም የተነሳ።/ፎቶ- ኤፒ ሙሉ ጌታ አያና

ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድምበር በከፊል መዝጋቷን ሱና የተሰኘ የሱዳን ዜና ወኪል ዘግቧል። ድምበር መዝጋቱን ሐሙስ ዕለት ያሳወቁት የሃገሪቱ ዋና ጸሐፊ እና ከሳላ የተሰኘው የሱዳን ክፍለ ግዛት አስተዳዳሪ የሆኑት ፋታል ራህማን አል-አሚን ናቸው።

ባለሥልጣኑ ጥገኝነት ለመጠየቅ ሱዳን የሚገኙ ስደተኞችን በተለመለከት ሀገሪቱ ምን እንደምታደርግ ገና የሚወሰን መኾኑንም ገልፀዋል። ሱዳን ይህን እርምጃ የወሰደችው በሰሜን ኢትዮጵያ፣ የትግራይ እና የፌደራሉ መንግሥት ጦርነት መግባታቸውን ተከትሎ ነው። የኢትዮጵያ አየር ሀይል በትግራይ የሚገኙ ወታደራዊ ተቋማትን አርብ ዕለት በቦምብ መምታቱም ተዘግቧል።

ያሳለፍነው ዕረብ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አሕመድ የትግራይ መንግሥት በመቀሌ ከተማ የሚገኝ የፌደራል መከላከያ ላይ ጥቃት ከፍቷል በሚል ወታደሮች ወደ ስፍራው እንዲንቀሳቀሱ ማዘዙ ይታወሳል።

XS
SM
MD
LG