በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“በመልሶ ማልማት በሚል ምክንያት ማፈናቀል ከለውጡ በኋላ ቆሟል” ምክትል ከንቲባ አቶ ታከለ ኡማ


ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት የኮሙኒኬሽን እና መረጃ ዳይሬክቶሬት የተገኘ
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት የኮሙኒኬሽን እና መረጃ ዳይሬክቶሬት የተገኘ

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን “መልሶ ማልማት በሚል ምክንያት ማፈናቀል ከለውጡ በኋላ ቆሟል” ብለዋል ምክትል ከንቲባ አቶ ታከለ ኡማ። 

ከንቲባው በተለይ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር ባደረጉት አጭር ቃለ ምልልስ "አርሶ አደሩን ያቀፈች ከተማ እንገነባለን" ብለዋል።

መሬታቸው ለልማት ከተወሰደባቸው የአዲስ አበባ አርሶአደሮች መካከል ሃያ ሁለት ሺህ የሚሆኑት የኮንዶሚኒየም ዕጣ ውስጥ እንዲገቡ መደረጉንም ከንቲባው አስታውቀዋል።

በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ባጠቃላይ ከ 60 ሽህ በላይ አባወራ አርሶ አደሮች መኖራቸው በጥናት ተረጋግጧል” ብለዋል አቶ ታከለ።

“በመልሶ ማልማት በሚል ምክንያት ማፈናቀል ከለውጡ በኋላ ቆሟል” ምክትል ከንቲባ አቶ ታከለ ኡማ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:35 0:00


XS
SM
MD
LG