ዋሽንግተን ዲሲ —
ከሰሞኑ ከመላው ኢትዮጵያ የተላኩ የቡና ናሙናዎች አዲስ አበባ ላይ መዓዛቸው ሲለካ፣ ጣዕማቸው ሲወዳደር ሰንብቷል።ይህ Cup of excellence የተሰኘ የላቀ ጣዕም ያላቸውን የቡና ዐይነቶች የማወዳደር መርሃ-ግብር ልዩ ጣዕም ያላቸውን ቡናዎች የማስተዋወቅ፣ የተሻለ ገበያ ዕድል እንዲያገኙ ማገዝ ዓላማው እንደሆነ አስተባባሪው ተቋም ይፋ አድርጓል።
ሀብታሙ ስዩም ውድድሩን የማስተባበር ኃላፊነት ከተሰጣት ቅድስት ሙሉጌታ ጋር ያደረገውን ምጥን ቆይታ ያዳምጡ።