በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“የጭራ ዲፕሎማሲ”


በኬንያ አዲሱ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ ዓለም የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ባቀረቡበት ወቅት
በኬንያ አዲሱ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ ዓለም የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ባቀረቡበት ወቅት

በኬንያ አዲሱ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ ዓለም የሹመት ደብዳቤያቸውን ለኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ሲያቀርቡ በእጃቸው ስለያዟት “ጭራ” ጉዳይ ተጨዋውተዋል። ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ፤ “የቀድሞው የኢትዮጵያ ንጉስ አፄ ኃይለስላሴ ለአባቴ የሰጧቸው ጭራ እስከመጨረሻ የሕይወት ፍፃሜያቸው ድረስ አብሯቸው ነበር” ሲሉም ነግረዋቸዋል።

አቶ መለስ ይህን የሹመት ደብዳቤ ይዘው ወደ ኬንያ የተጓዙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነውና ቢሾፍቱ አቅራቢያ የወደቀው በበረራ ቁጥር ኢቲ 302 ቦይንግ 737 ማክስ ኤይት አይሮፕላን ከተነሳ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነበር። በዚህ አውሮፕላን ሳይበሩ የቀሩት ደግሞ እናታቸውን ተሰናብተው ለመውጣት ጉዟቸውን በሰዓታት በማራዘማቸው እንደሆነ ነግረውናል።

(ከአቶ መለስ ዓለም ጋር ያደረግነውን ቃለምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

“የጭራ ዲፕሎማሲ”
please wait

No media source currently available

0:00 0:18:59 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG