ሰሜናዊ ማሊ ውስጥ የምትኖር አንዲት የስዊስ ዜጋ ከመኖሪያ ቤቷ መጠለፏ ተገለጸ

ፋይል ፎቶ ቢያትርስ ስቶክሊ (Beatrice Stockly)በአክራሪ እስልምና ተከታዮች ተጠልፋ ከነበረችበት ቦታ ወደ ትምቡክቱ ስትገባ እአአ 2012

በአርባዎች ዕድሜ ክልል የምትገነው ስቶክሊ ሚሶናዊ ስትሆን፣ እአአ በ2012ም በአክራሪ እስልምና ተከታዮች ተጠልፋ እንደነበር ታውቋል።

ሰሜናዊ ማሊ ውስጥ የምትኖር አንዲት የስዊስ ዜጋ ከመኖሪያ ቤቷ መጠለፏ ተገለጸ፣ ይህም በአራት ዓመት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ነው።

ቲምቡክቱ (Timbuktu) የሚገኙ ነዋሪዎችና ባለሥልጣናት እንዳስረዱት፣ ታጣቂዎች በዛሬው ቀን ወደ ቢያትርስ ስቶክሊ (Beatrice Stockly) መኖርያ ቤት በመግባት ይዘዋት ሄደዋል። ለጠለፋው ተጠያቂ ነኝ ያለ ወገን እስካሁን አልቀረበም።

በአርባዎች ዕድሜ ክልል የምትገነው ስቶክሊ ሚሶናዊ ስትሆን፣ እአአ በ2012ም በአክራሪ እስልምና ተከታዮች ተጠልፋ እንደነበር ታውቋል።

የስዊስ መንግሥት ጠለፋውን እንደሚያውቅ በመግለጽ፣ ተጨማሪ ዝርዝር አልሰጠም። የዜና ዘገባ አለን ከዚህ በታች ካለው ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ሰሜናዊ ማሊ ውስጥ የምትኖር አንዲት የስዊስ ዜጋ ከመኖሪያ ቤቷ መጠለፏ ተገለጸ