ከ700 በላይ ፍልሰተኞች ሜዲትሬንያንን ለማቋረጥ ሲሞከሩ መስጠማቸው ተነገረ

Your browser doesn’t support HTML5

በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ከሞት የተረፉ ፍልሰተኞችን የጫነው የኢጣልያ ባሕር ኃይል መርከብ፣ ትናንት እሑድ ነው ረጅዮ ባላብርያ ወደብ ላይ የደረሰው። የሜዲትሬንያንን ባሕር ለማቋረጥ ሲሞክሩ ሕይወታቸውን ያጡ የ45 ሰዎች አስከሬንም አብሮ ተጭኗል። ከሞት የተረፉትና ብዙዎቹ ነጭ የለበሱት ፍልሰተኞች ከመርከቧ ሲወርዱ፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ተቀብለዋቸዋል።