"በምንጃር ግጭት ሁለት ሰዎች ቆስለው አንድ ሞቷል" - የምንጃር ነዋሪ

  • ቆንጂት ታየ

ምንጃር

በአማራ ክልል በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር ለ15 ቀናት ያህል መብራት በመጥፋቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ያካሄዱት የተቃውሞ ሰልፍ ወደ ግጭት ማምራቱንና ግጭቱን ተከትሎም ከሰልፈኞቹ በአንዳንዶቹ ላይ የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸውና በተጨማሪም ከአረርቲ ከተማ ወጣ ብሎ የሚገኝ የችፑድ ማምረቻ ፋብሪካ ቃጠሎ የደረሰበት መሆኑን ትናት ምሽት ዘግበናል።

በአማራ ክልል በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር ለ15 ቀናት ያህል መብራት በመጥፋቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ያካሄዱት የተቃውሞ ሰልፍ ወደ ግጭት ማምራቱንናግጭቱን ተከትሎም ከሰልፈኞቹ በአንዳንዶቹ ላይ የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸውና በተጨማሪም ከአረርቲ ከተማ ወጣ ብሎ የሚገኝ የችፑድ ማምረቻ ፋብሪካ ቃጠሎ የደረሰበት መሆኑን ትናት ምሽት ዘግበናል ። ዛሬ በስልክ ያነጋገርናቸው ነዋሪ

“ሁለት ሰዎች መቁሰላቸውንና አንደኛው ሞቷል የሚል ሰምቻለሁ” ብለውናል።

የወረዳው አስተዳዳሪ በበኩላቸው የሰዎቹን መቁሰል አረጋግጠው የአንደኛውን መሞት ግን ለጊዜው አላወቅኩም ብለውናል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

"በምንጃር ግጭት ሁለት ሰዎች ቆስለው አንድ ሞቷል" - የምንጃር ነዋሪ