የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር የቱርክ የጦር ሓይሎች ከኢራቅ እንዲወጡ አሳሰቡ

  • ቆንጂት ታየ
የቱርክ የጦር ሓይሎች ከኢራቅ በአስቸኩዋይ መውጣት አለባቸው በማለት የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ጥሪ አቅርበዋል።

የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይደር አል አባዲ (Haider al-Abadi)የቱርክ የጦር ሓይሎች ከኢራቅ በአስቸኩዋይ መውጣት ኣለባቸው ሲሉ በድጋሚ አሳሰቡ።

ቱርክ ወታደራዊ አሰልጣኝዎችዋን ስለምን ወደ ኢራቅ ድንበሮች አዝልቃ ትልካለች?
የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይደር አል አባዲ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ረቡዕ ከቱርክ ጠቅላይ ሚኒስትር አህመት ዳቩቶጉሉ (Ahmet Davutoglu)ጋር በቴሌፎን ሲነጋግሩ፣ "የእስልምና መንግሥት ነኝ የሚለው ቡድን ተዋጊዎች ቱርክና ሶሪያ ድንበር ላይ ናቸው እየተባለ ቱርክ ወታደራዊ አሰልጣኝዎችዋን ስለምን ወደ ኢራቅ ድንበሮች አዝልቃ ትልካለች?” ሲሉ ጠይቀዋል። የዜና ዘገባችንን ከዚህ በታች ካለው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር የቱርክ የጦር ሓይሎች ከኢራቅ እንዲወጡ አሳሰቡ