ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋራ የተደረገውን የመግባቢያ ስምምት በተመለከተ፣ በማኅበራዊ የመገናኛ አማራጮች የሐሰት መረጃዎች እየተሰራጩ ናቸው፤ ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል፡፡
SEE ALSO: ኢትዮጵያና ሶማሌላንድ የባሕር በር ውል ቋጠሩኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ለመሰረዝ እንደወሰነች”
“ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ለመሰረዝ እንደወሰነች” የሚገልጽ ይዘት ያለው መረጃ መሰራጨቱን ተከትሎ፣ ትላንት ረቡዕ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መግለጫ ሰጥቷል፡፡
The PMO advises the public to be cautious of fake content circulating online about an MOU with Somaliland. Official communications on local, regional, and int’l matters are only through PMO’s official channels. Stay vigilant against such fake content misusing our official logo.
— Office of the Prime Minister - Ethiopia (@PMEthiopia) June 26, 2024
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ የመግባቢያ ስምምነቱ የሚገኝበትን ደረጃ በተመለከተ “ወቅቱ ሲደርስ ይገለጻል” ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡
በተያያዘ ቃል አቀባዩ፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ ግዛት ጥሰው እንደገቡ፣ በሶማሊያ በኩል የቀረበውን ክስም “ሐሰት ነው” ሲሉ አጣጥለዋል፡፡
Your browser doesn’t support HTML5