የኦሮሚያ ክልል ፍትሕ ቢሮ ግድያው በስሕተት የተፈፀመ ነው ብሎ እንደማያምን አስታወቀ

ወደ ኬንያ ሞያሌ የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን

የኦሮሚያ ክልል ፍትሕ ቢሮ በሞያሌ ከተማ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈፀመው ግድያ በስሕተት የተፈፀመ ነው ብሎ እንደማያምን አስታወቀ።

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በበኩሉ፤ ጉዳዩን ዓለም ሊያውግዘው የሚገባ በአካባቢው እንደተባለው ኦነግ ቢኖር እንኳን ከማሰር የዘለለ እርምጃ ሊወሰድ አይገባም ነበር ብሎታል።

ከመስከረም ወር ወዲህ ብቻ እንኳን ተደጋጋሚ የጅምላ ግድያዎች እየተፈፀመ ነውም ብሏል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከዚህ ቀደም የሚነሱትንም ሆነ የአሁኑን በተመለከተ ሪፖርት አጠናቅሮ ዝግጁ ማድረጉን ገልፆ ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች በመሆኑ ለማቅረብ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የኦሮሚያ ክልል ፍትሕ ቢሮ ግድያው በስሕተት የተፈፀመ ነው ብሎ እንደማያምን አስታወቀ

በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በሞያሌ ከተማ “ሸዋበር” በተባለ የመኖሪያ መንደር በትናንትናው ዕለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በፈፀሙት ጥቃት ዐሥር ሰዎች ተገድለው ሌሎች ዐሥራ አንድ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች፣ የከተማው አስተዳደርና ኮማንድ ፖስቱ አረጋግጠዋል። ይህን በተመለከተ የቀደመውን ዘገባ ለማድመጥ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

የዘገባውን የእንግሊዘኛ ቅጂ ለማንበብ ደግሞ ማስፈንጠሪውን ይጫኑ።