አፍጋኒስታን፣ ቻይና እና ዩናይትድ ስቴትስ የሚካፈሉበት ድርደር በፓኪስታን እየተካሄደ ነው። ፓኪስታን የአፍጋኒስታንን የሰላም ሂደት ለማንሰራራት ስለሚቻልበት መንገድ የሚነጋገር የአራትዮሽ ድርድር በማስተናገድ ላይ ነች ።
የፓኪስታን ጠቅላይ ምኒስትር ናዋዝ ሻሪፍ የውጭ ጉዳይ አማካሪ ሳርታዥ ኣዚዝ ውይይቱን በንግግር ከፍተዋል።
የዕርቀ ሰላሙ ሂደት ዋና ዓላማ ታሊባኖቹን ወደድርድሩ ጠረጴዛ እንዲመጡ ማድረግና የፖለቲካ ግባቸውን ለማሳካት ሁከትን እንዳይጠቀሙ ማበረታቻ መስጠት ነው ብለዋል።
የአፍጋኒስታን ጸጥታ ሃይሎች ከታሊባን ዓመጽ ተዋጊውችት ጋር በ ባልክ (Balkh)ክልል ኩንዱዝ (Kunduz) ከተማ ሰሜን ካቡል (Kabul)ውስጥ እየተዋጉ እአአ 2015
አፍርጋኒስታን ውስጥ ባለፈው አንድ ዓመት የታሊባን ዓመጽ እየተስፋፋ መምጣቱ ጦርነት በበጣጠቃት ሃገር የባሰ ደም መፋሰስና አለመረጋጋት ይመጣል የሚል ስጋት ፈጥሯል። የዜና ዘገባችንን ለማዳመጥ ከዚህ በታች ያለውን የድምጽ ፋይል ይጫኑ።
Your browser doesn’t support HTML5
የአፍጋኒስታንን የሰላም ሂደት የሚያነጋግር የአራትዮሽ ድርድር በፓኪስታን