የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ መፈታት የዘገየው፣ ማረሚያ ቤቱ “ሰነድ አልደረሰኝም” በማለቱ እንደነበር ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ፡፡
አዲስ አበባ —
የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ መፈታት የዘገየው፣ ማረሚያ ቤቱ “ሰነድ አልደረሰኝም” በማለቱ እንደነበር ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ፡፡
የተመሰረተባቸው የሽብር ክሥ በሌሉበት ከታየ በኋላ፣ የሞት ፍርድ ተላልፎባቸው የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፣ ዛሬ ከቃሊቲ ወኅኒ ተለቀው አባታቸው ቤት ሲደርሱ በአካባቢው ተሰብስቦ ሲጠባበቅ የነበረ ብዙ ቁጥር ያለው ደጋፊያቸው፣ በከፍተኛ ደስታና ሆታ ሲቀበሏቸው፣ እንደተደሰቱ ቢናገሩም፣ ሌሎች ብዙ ያልተፈቱ መኖራቸውን ግን እንደሚያሳዝናቸው ገልፀዋል፡፡
ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር ሌሎችም ከ5መቶ በላይ እሥረኞች በምህረትና ክሳቸው እየተቋረጠ ተለቀዋል፡፡
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከቪኦኤ ጋር