በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ረሃብ በአፍሪካ

ዓርብ 17 ሜይ 2024

Calendar
ሜይ 2024
እሑድ ሰኞ ማክሰ ረቡዕ ሐሙስ ዓርብ ቅዳሜ
28 29 30 1 2 3 4
5 6 7 8 9 10 11
12 13 14 15 16 17 18
19 20 21 22 23 24 25
26 27 28 29 30 31 1
በምግብ እጦት የሚሰቃዩ ሱዳናውያን ህጻናት በMSF ክሊኒክ እየታከሙ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ፤ በሜቼ ካምፕ፣ ቻድ፣ እአአ ሚያዝያ 6/2024
በምግብ እጦት የሚሰቃዩ ሱዳናውያን ህጻናት በMSF ክሊኒክ እየታከሙ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ፤ በሜቼ ካምፕ፣ ቻድ፣ እአአ ሚያዝያ 6/2024

በጦርነት በተጎዱት የሱዳን አካባቢዎች ቁጥሩ ወደ አምስት ሚሊዮን በሚጠጋ ህዝብ ላይ የተደቀነው የረሃብ ቸነፈር አደጋ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ ነው ሲል የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስጠነቀቀ። በዚህ ሳምንት ሱዳንን ጎብኝተው የተመለሱት የዓለም የምግብ ፕሮግራም ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ካርል ስካዉ ትናንት ረቡዕ ባወጡት መግለጫ የረሃቡ ሁኔታ በፍጥነት እያሽቆለቆለ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የከበደ ቸነፈር አፋፍ ላይ ለሚገኘው ህዝብ የሰብዓዊ ረድዔት ተደራሽነትን እናመቻቻለን ብለው ቃል የገቡት ወገኖች በሙሉ አሁኑኑ በተግባር ሊተረጉሙት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ዳርፉር እና ኮርዶፋን አካባቢ የክረምቱ ዝናብ ወቅት ገብቶ መንገዶች ከመዘጋጋታቸው በፊት የምግብ አቅርቦት ለማከማቸት ያለው የጥቂት ሳምንታት ጊዜ ብቻ መሆኑን የዓለም የምግብ ፕሮግራም ባለስልጣኑ መግለጫ አስጠንቅቋል፡፡ ገበሬዎችም ዝናቡ ከመጀመሩ አስቀድሞ ደህንነታቸው ተጠብቆ የእርሻ መሬታቸው ደርሰው መዝራት እንደሚኖርባቸው አክለዋል፡፡

የዓለም የምግብ ፕሮግራም የውጊያው መቀጠል የድንበር ኬላዎች መዘጋት እና ፍተሻን የመሳሰሉ ችግሮች ቢኖሩም በአሁኑ ጊዜ ሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ለሚሆኑ ሱዳናውያን እርዳታ እያቀረበ መሆኑን ገልጿል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰሜናዊ ዳርፉር ያለው ሁኔታ ባለፉት ሳምንታት እየተባባሰ መሆኑን ተመድ በማስጠንቀቅ ላይ ነው፡፡ ባለፉት ቀናት የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች ዋና ከተማዋ ኤል ፋሸር ወደሚገኙት የሱዳን የጦር ሠራዊት ኃይሎች መገስገስ መጀመራቸውን ዘገባዎች አመልክተው ከተማዋ ያሉት ከ8 መቶ ሺህ በላይ ሲቪሎች አደጋ ላይ እንዳሉ ገልጠዋል፡፡

ባለፈው ሰኞ የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ ተፋላሚዎቹ ወገኖች በአስቸኳይ ውጊያውን አቁመው የተኩስ አቁም ድርድሩን እንዲቀጥሉ ጥሪ አሰምተዋል፡፡

ዳርፉር ውስጥ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ያልተያዘች ከተማ ኤልፋሸር ብቻ ነች፡፡ ኤል ፋሸር ላይ የለየለት ውጊያ ከተቀሰቀሰ እአአ በ2000 ዓም ዳርፉር ውስጥ የአረብ ጃንጃዊድ ታጣቂዎች በዛግዋ፡ ማሳሊት ፡ ፉር እና ሌሎችም አረብ ያልሆኑ ጎሣዎች ላይ የፈጸሙትን የዘር ማጥፋት የመሰለ ጭካኔ የተመላበት ጥቃት ሊደርስ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡

ኤል ፋሸር ውስጥ በምግብ ዕጥረት እና በዋጋው ማሻቀብ የተነሳ 330 ሺህ ህዝብ ለከባድ የረሐብ ቀውስ መጋለጡን ተ መ ድ አስታውቋል፡፡

ፎቶ ፋይል፦ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ፎቶ ፋይል፦ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በግጭት ለምትታመሰው፣ በጎርፍ እና ድርቅ ለተጠቃችው ኢትዮጵያ የሚያስፈልገውን የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦት ከፍ ለማድረግ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ማቀዱን ዛሬ ማክሰኞ አስታወቀ።

ከኢትዮጵያ እና ከእንግሊዝ መንግሥታት ጋራ በመተባበር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጄኔቫ ላይ ያካሄደው የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ለ15.5 ሚሊዮን ሰዎች የሚሆን የነብስ አድን ርዳታ እና ለተጨማሪ 10 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሰዎች የሚሰጠውን የምግብ ዕርዳታ መጠን ለማሳደግ የታለመ መሆኑ ተመልክቷል።

“የአስቸኳይ ርዳታ የሚጠይቁት ሁኔታዎች በድርቅ እና በጎርፍ እንዲሁም በግጭት እየተባባሱ የመጡ ናቸው” ሲል ተመድ አስታውቋል።

"ኤልኒኞ በሰሜናዊ የሃገሪቱ ክፍል በሚገኙ ደጋማ አካባቢዎች ያለውን ድርቅ በማባባሱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የውሃ አቅርቦት ዕጥረት፤ የግጦሽ ሳር እጦት እና የምርት መጠን ማሽቆልቆል ያስከተሏቸውን ፈተናዎች ለመቋቋም እየተጣጣሩ ነው" ብሏል።

በዚህ ዓመት በግጭቶች እና የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተሏቸው ችግሮች የተነሳ ቁጥራቸው ከ21 ሚሊየን በላይ የሚደርሱ ሰዎች በኢትዮጵያ ሰብአዊ ርዳታ እንደሚፈልጉ የገለጸው ኦቻ፣ ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት ወራት ቁጥራቸው 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን የሚደርስ ሰዎች ለከፋ የምግብ ዋስትና ዕጥረት መጋለጣቸውንም ገልጿል።

በተያያዘ እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ርዳታ መጠን ለማሳደግ ተጨማሪ 100 ሚሊዮን ፓውንድ (124 ነጥብ 58 ሚሊዮን ዶላር) እንደምትሰጥ አስታውቃለች።

በብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር አንድሪው ሚሸል ሲናገሩ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ርዳታ ለመስጠት የተገባው ቃል የባህረ ሰላጤውን አገሮች ጨምሮ “ሌሎች ሃገራት እንዲሳተፉ ያበረታታል” የሚል እምነት እንዳደረባቸው ተናግረዋል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG