በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዚምባብዌ ሃኪሞች የኑሮ መሻሻልና የደመወዝ ክፍያ ጥያቄ


በዚምባብዌ የመንግሥት ሆስፒታል የሚሰሩ ነባር ሃኪሞች መንግሥት የኑሮ መሻሻልና የደመወዝ ክፍያ ጥያቄያቸውን ካላሟላ ከዛሬ አንስቶ አድማ ለመጀመር ዝተዋል።

ከአንድ ወር በፊት አንስተው ተመሳሳይ ጥያቄዎችን በማንሳት አድማ ላይ ከቆዩት በመቶዎች የሚቆጠሩ የሥራ ባልደረቦችቻው ጋር ይቀላቀላሉ ። በደቡባዊት አፍሪካይቱ ሃገር ባለው የተራዘመ የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በሰራተኞች፣ በህክምና መሳርያዎችና አቅርቦቶች እጥረት ምክንያት በሽተኞች በመንግሥት ሆስፒታሉ ለመታከም አለመቻላቸው ተገልጿል።

የነባር የሆስፒታል ሀኪሞች ማኅበር ባወጣው መግለጫ "በሚዘገንንና አሳፋሪ በሆነው የሥራ ሁኔታ" ምክንያት ለመስራት አለመቻላችንን በይፋ ከመግለፅ ሌላ አማራጭ የለንም” ይላል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG