በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የወላይታ ዞን አመራር አባላትን ጨምሮ የ26 ሰዎች እስር


“ከህወሓትና ከኦነግ ጋር ተመሳጥረው ሃገር ለማፍረስ እየሠሩ ናቸው” ያላቸውን የወላይታ ዞን አመራር አባላትን ጨምሮ ሃያ ስድስት ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት አስታውቋል።

ይህንን ተከትሎ በዞኑ ዋና ከተማ ሶዶና ቦዲቲ ከተማ ውስጥ ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር በተፈጠረ ግጭት ህይወት መጥፋቱን የዐይን እማኝ ነን ያሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

አካባቢውን የመከላከያ ሠራዊት መቆጣጠሩን ነዋሪዎች ገልፀው ሃገር አቋራጩን አውራ ጎዳና ጨምሮ ወላይታ ሶዶን ከሰባት አከባቢዎች ጋር የሚያገናኙ መንገዶች ትናንት ማምሻውን ጀምሮ መዘጋታቸውን ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የወላይታ ዞን አመራር አባላትን ጨምሮ የ26 ሰዎች እስር
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:46 0:00


XS
SM
MD
LG