ባለፈው ሳምንት የእርዳታ አቅርቦት የጫኑ 165 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል መድረሳቸውንና 94 ተሽከርካሪዎች ደግሞ በጉዞ ላይ መሆናቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታውቋል። የድርጅቱን መረጃ ያረጋገጡት የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ፣ ከዚህም ውጭ በአየር እና በየብስ የሚደረገው የእርዳታ አቅርቦት መቀጠሉን አብራርተዋል፡፡ይሁንእንጂ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ያለው የዕርዳታ አቅርቦት ከሚያስፈልገው አንጻር እጅግ አነስተኛ መሆኑን እና በዚህም ምክንያት ሞትና ረሃብ እየተስፋፋ እንደሚገኝ የትግራይ ክልል የግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ኃላፊ መሆናቸውን የገለጹት ዶ/ር አትንኩት መዝገቡ፣ በቅርቡ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡ ወደ ክልሉ ለሚደረገው የዕርዳታ አቅርቦት ማነስ የትግራይ ክልል አመራሮች እና አንዳንድ የረድኤት ድርጅቶች መንግስትን ተጠያቂ ቢያደርጉም፣ መንግሥት ግን ውንጀላውን አይቀበልም፡፡
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ሴፕቴምበር 29, 2023
በዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ዳያስፖራ አማካሪዋ ለአህጉሪቱ ያላቸውን ትኩረት ይናገራሉ
-
ሴፕቴምበር 29, 2023
ፕሬዚዳንት ባይደንን ለመክሰስ የመጀመሪያው የይፋ ምስክርነት ተሰማ
-
ሴፕቴምበር 29, 2023
የትዕግሥት አሰፋ የማራቶን ክብረ ወሰን “ከዘንድሮ ውጤቶች ሁሉ ታላቁ ነው” ሲል ፌዴሬሽኑ ገለጸ
-
ሴፕቴምበር 29, 2023
ጆ ባይደን በትራምፕ ላይ የሚሰነዝሩትን ትችት አጠናክረው ቀጥለዋል
-
ሴፕቴምበር 29, 2023
የጋቦን ወታደራዊ አመራር ለለውጥ ግፊት የሚያደርጉ ጋቦናውያን እንዲታገሡ ጠየቀ
-
ሴፕቴምበር 29, 2023
መንግሥት ለትግራይ ክልል ተፈናቃዮች አስቸኳይ የምግብ ርዳታ መላክ እንደ ጀመረ ተገለጸ