በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች አንዳንድ ወረዳዎች የከፋ ረኀብ ተጋርጦባቸዋል


የምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች አንዳንድ ወረዳዎች የከፋ ረኀብ ተጋርጦባቸዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:45 0:00

የምዕራብ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች አንዳንድ ወረዳዎች የከፋ ረኀብ ተጋርጦባቸዋል

በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች አንዳንድ ወረዳዎች፣ ረኀብ እንደተጋረጠባቸው፣ ነዋሪዎች ገለጹ።

የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው የወረዳዎቹ ነዋሪዎች፣ በመንግሥት እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል ለዓመታት በዘለቀው ግጭት የተነሳ ለከፋ ረኀብ እንደተጋለጡ ተናግረዋል።

ከፍተኛ የሰብአዊ ርዳታ እጦት እንዳለባቸው ነዋሪዎቹ ጠቅሰው፣ አሁንም በርካታ የወረዳዎቹ ሕፃናት፣ በረኀብ እየተሠቃዩ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

በጉዳዩ ላይ፣ ከምዕራብ ወለጋ እና ከቄለም ወለጋ ዞኖች የጤና ተቋማት እና ቡሳ ጎኖፋ እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ኮምዩኒኬሽን ቢሮ እና ቡሳ ጎኖፋ፣ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG