ተቋሙ በአርሲ በቆጂ እና በወላይታ ሶዶ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ልጃገረዶች በአትሌቲክስ እንዲሳተፉ በትጥቅ እና በስልጠና በማገዝ እንዲሁም በምግብ፣ በትምህርት እና በሌሎች የሕይወት ክህሎት ሥልጠናዎችን በመስጠት ያበቃል።
በተጨማሪም ለእናቶች የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት በማዘጋጀት ሴቶች እራሳቸውን እንዲችሉ ያግዛል። ኤደን ገረመው የተቋሙን የሶዶ ሥራ አስኪያጅ እና ተጠቃሚዎችን አነጋግራ ተከታዩን ዘገባ አዘጋጅታለች።