በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሃይማኖት ተኮር ዘገባዎች የብዙኀን መገናኛዎችን ሚና የዳሰሰው ጥናት


 በሃይማኖት ተኮር ዘገባዎች የብዙኀን መገናኛዎችን ሚና የዳሰሰው ጥናት
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:23 0:00

ባለፉት አምስት ዓመታት፣ የኢትዮጵያ ብዙኀን መገናኛዎች ያጠናቀሯቸውን ሃይማኖት ተኮር ዘገባዎች እና በኢትዮጵያ፣ ብዙኀን መገናኛዎች ከሃይማኖት ጋራ ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት የዳሰሰ “ሃይማኖት እና መገናኛ ብዙኀን በኢትዮጵያ” የሚል ጥናት በቅርቡ ይፋ ሆኗል። ጥናቱ  በኖርዌይ ኦስሎ ሜት ዩኒቨርሲቲ የተግባቦት መምህራን በኾኑት ተባባሪ ፕሮፌሰር ሙላቱ ዓለማየሁ እና የሥራ ባልደረባቸው ፕሮፌሰር ቴሬ ሸዳል የተዘጋጀ ነው።

ሁለቱ ምሁራን ከዚኽ ቀደም፣ “ብሔር እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን” የሚል ጥናት አቅርበዋል፡፡ የአሁኑ ጥናትም፣ የብሔር ጠርዘኝነት የሚታይባቸው ብዙኀን መገናኛዎች፣ በሃይማኖት እና እምነት ተኮር ዘገባዎች ረገድ ያላቸውን ሚና የቃኘ ነው።

XS
SM
MD
LG