ከዐማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ ዝርዝር መረጃዎችን ለማካተት ያደረግነው ጥረት ባይሳካም፣ ዐዲሱ የዐማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፣ የጸጥታ ስጋቱ በመኸር ሰብል ልማት ላይ ተጽእኖ እንዳሳደረ፣ ከካቢኔያቸው ጋራ ባካሔዱት ውይይት አረጋግጠዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የመከላከያ እና የፋኖ ትጥቃዊ ግጭት በግብርናው ላይ ተጽእኖ እንዳስከተለ ተገለጸ
በዐማራ ክልል በአገሪቱ የመከላከያ ኀይል እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተስፋፋው ትጥቃዊ ግጭት፣ በግብርና ሥራቸው ላይ ተጽእኖ እንደፈጠረባቸው፣ በሰሜን ሸዋ እና በደቡብ ወሎ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮች አስታወቁ፡፡ ከዘገየው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በተጨማሪ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የተስፋፋው የትጥቅ ግጭት፣ የእርሻ ማሳቸውን በትኩረት እንዳይንከባከቡ እያናጠባቸው እንዳለና ለምርት እጥረትም ሊዳርጋቸው እንደሚችል፣ አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ዲሴምበር 07, 2023
ከፍልሰት ተመላሽ ወጣት ኢትዮጵያውያን የጉዞ ሠቆቃቸውን ያጋራሉ
-
ዲሴምበር 07, 2023
የዘንድሮው የዱባዩ የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ እና እሰጥ አገባው
-
ዲሴምበር 07, 2023
አሜሪካ ከሩሲያ ጋራ ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ ወታደሮችን በጦር ወንጀል ከሰሰች
-
ዲሴምበር 07, 2023
በ“አሌክሳንድሪያ ስካትሽ የገና የጎዳና በዓል” ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳተፉ
-
ዲሴምበር 07, 2023
በናይጄሪያ የካዱና ግዛት የቦምብ ጥቃት በጥልቀት እንዲመረመር ፕሬዚዳንቱ አዘዙ