ከዐማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ ዝርዝር መረጃዎችን ለማካተት ያደረግነው ጥረት ባይሳካም፣ ዐዲሱ የዐማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፣ የጸጥታ ስጋቱ በመኸር ሰብል ልማት ላይ ተጽእኖ እንዳሳደረ፣ ከካቢኔያቸው ጋራ ባካሔዱት ውይይት አረጋግጠዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የመከላከያ እና የፋኖ ትጥቃዊ ግጭት በግብርናው ላይ ተጽእኖ እንዳስከተለ ተገለጸ
በዐማራ ክልል በአገሪቱ የመከላከያ ኀይል እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተስፋፋው ትጥቃዊ ግጭት፣ በግብርና ሥራቸው ላይ ተጽእኖ እንደፈጠረባቸው፣ በሰሜን ሸዋ እና በደቡብ ወሎ ዞኖች የሚገኙ አርሶ አደሮች አስታወቁ፡፡ ከዘገየው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በተጨማሪ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የተስፋፋው የትጥቅ ግጭት፣ የእርሻ ማሳቸውን በትኩረት እንዳይንከባከቡ እያናጠባቸው እንዳለና ለምርት እጥረትም ሊዳርጋቸው እንደሚችል፣ አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ሴፕቴምበር 22, 2023
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ለጦር ዘመቻቸውና ለሰላም ዕቅዳቸው ድጋፍ ፍለጋ እየጣሩ ነው
-
ሴፕቴምበር 22, 2023
“በዓለም የሰላም ቀን” የሴቶች ወሳኝ ተሳትፎ ጎልቶ ወጥቷል
-
ሴፕቴምበር 22, 2023
በቅበት የሃይማኖት ግጭት ተጠርጣሪዎች በሕግ እንዲጠየቁ ኢሰመጉ አሳሰበ
-
ሴፕቴምበር 22, 2023
እያየለ ባለው የአል-ሻባብ ጥቃት ላይ የሶማሊያ ጎረቤቶች ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ
-
ሴፕቴምበር 22, 2023
በአዋሽ አርባ ታስረው የቆዩ የትግራይ ተወላጅ የመከላከያ አባላት እንደተፈቱ ተገለጸ
-
ሴፕቴምበር 22, 2023
ያልተጨለፈውን የደምበል ሐይቅ ዕምቅ ሀብት ለማልማት እየተሠራ ነው