በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዲሞክራቲክ ኮንጎ ግጭቱ ተባብሶ ቀጥሏል


በዲሞክራቲክ ኮንጎ ግጭቱ ተባብሶ ቀጥሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:19 0:00

በሩዋንዳ የሚደገፉት ኤም 23 ተብለው የሚታወቁት የአማጺ ቡድኖች የዴሞክራቲክ ኮንጎ ቁልፍ ከተማ የሆነችውን ምሥራቃዊ ጎማን ትላንት ሰኞ ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠራቸውን ተከትሎ፤ በዴሞክራቲክ ኮንጎ አለመረጋጋት እና ሁከት ሰፍኗል። በዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ተቃዋሚዎች በሩዋንዳ፣ ፈረንሳይ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ኬኒያ ኤምባሲዎች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።

ጎማ ውስጥም ዝርፊያ፣ አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በመሣሪያ ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታሎች እንደሚገኙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።

የመንግሥታቱ ድርጅት በዴሞክራቲክ ኮንጎ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ እና ወደ ውይይት እንዲገባም ጥሪ አቅርቧል።

XS
SM
MD
LG